ግዢ
በሁሉም ከተሞች እንዲሁም በብዙ መንደሮች ውስጥ ሱፐርማርኬቶች አሉ፡፡ እዚያ ብዙውን ጊዜ ለዕለት ተዕለት ሕይወት አስፈላጊ የሆኑትን ሁሉ ማለትም ዳቦ፤ ስጋ፤ ፍራፍሬ እና አትክልት፤ ወተት እና እርጎ፤ቸኮሌት፤የጽዳት እቃዎች፤ የሽንት ቤት ወረቀቶች እና ሌሎች ብዙ ነገሮችን ማግኘት ይችላሉ። በጀርመን ሀገር ውስጥ ያሉ ሱቆች የመክፈቻ ሰዐታቸው የተለያየ ነው፡፡ ሱፐርማርኬቶች ብዙውን ጊዜ ከጠዋቱ 7:00 እስከ ማታ 8:00 ድረስ ክፍት ናቸው።